የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማል የ2014 የልዩ ልዩ ስፖርታዊ ሻምፒዮና እና የባህል ስፖርት ውድድሮች መዝጊያ ላይ ባደረጉት ንግግር ስፖርት ሁሌም የሚሰራ እንጂ ተሰባስበን በመበተን የምናሸንፈው እና ተሸንፈን ቤት የምንገባበት ውድድር አይደለም ብለዋል።ዛሬ የተሸነፈ ነገ የሚያሸንፍ በመሆኑ ሁሌም በስፖርት የሚያሳልፉና በእዚህ የውድድር ሜዳ በመገኘት አቅማቸውን ላሳዩ መምህራን ፣ ብዙዎች ዋጋ ከፍለው የዋንጫ ባለቤት ለሆኑና በውድድሩ ድል ላልቀናቸው አሰልጣኞችና ተጫዋቾች ያላቸውን አክብሮት ገልጸዋል አቶ መሀመድ ።በተደረጉ ውድድሮች ዞኑን ወክለው የተመረጡ ተጫዋቾች የዞኑ አምባሳደሮች በመሆናቸው የዞኑን ባህልና እሴት ተላብሰው በቀጣይ በክልሉ በሚካሄዱ ውድድሮች አመርቂ ውጤት ማምጣት እንደሚጠበቅባቸው ዋና አስተዳዳሪው አሳስበዋል።አያይዘውም አቶ መሐመድ ታዳጊዎች በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ለማብቃት ዞናዊ ውድድር ከማዘጋጀት በተጨማሪ በውድድሩ የተሻለ እንቅስቃሴ የነበራቸው ተጫዋቾች በወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ እንዲታቀፉ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አወል ጅማቶ በበኩላቸው የስፖርቱ ቤተሰቦች በውድድሩ ያሳዩት ስፖርታዊ ጨዋነት ውድድሩ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስችሎታል ብለዋል።በተወዳዳሪዎቹ መካከል የነበረው ጠንካራ ፉክክር ተተኪ ስፖርተኞች ለመለየት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የተናገሩት ኃላፊው በቀጣይ በደቡብ ክልል የልዩ ልዩ ስፖርታዊ ሻምፒዮና የሚሳተፉ ስፖርተኞች ተመልምለዋል ብለዋል።የዞኑ ልዩ ልዩ ስፖርታዊ ሻምፒዮናው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የስፖርት ማህበራት፣ ዳኞችን፣ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደርና የመስቃን ወረዳ አስተዳደር እንዲሁም መላው የስፖርት ቤተሰብ የነበራቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ምስጋና አቅርበዋል። ኢንስትራክተር ቸሩ ጠበል በሰጡት አስተያየት ውድድሩ ፍጹም ሰላማዊ እና ስፖርታዊ ጨዋነት ተላብሶ እንዲጠናቀቅ የዳኞች አበርክቶ ከፍተኛ ነበር ብለዋል።በዞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዳኞች እንዳሉ የተናገሩት ኢንስትራክተር ቸሩ በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ ዳኞች ውድድሮቹ በብቃት መዳኘታቸውን ገልጸዋል።በእግር ኳስ ከፍተኛ ፉክክር የታየበት የጉንችሬ ከተማ እና የማረቆ ወረዳ ጨዋታ አስከ 90 ደቂቃ ባለው ጊዜ አንድ አቻ አጠናቀው በተሰጣቸው የቅጣት ምት ጉንችሬ ከተማ 3 ለ0 በሆነ ውጤት የማረቆ አቻውን አሸንፎ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል ።በተለያዩ ውድድሮች አሸናፊ የሆኑ ወረዳዎችና ተጫዋቾች የዋንጫና የሜዳልያ ሽልማት አግኝተው ውድድሩ ተጠናቋል። = ኢትዮጵያን እናልማ! = የፈረሰውን እንገንባ! = ለፈተና እንዘጋጅ! በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡ Facebook:- https://www.facebook.com/gurage1Zone Website:- https://gurage.gov.et Telegram:- https://t.me/comminuca Youtub: –https://www.youtube.com/channel/UCzrcazGvvIO2tG7bQN36Cx
- Our Visitor
- Today's visitors: 5
- Today's page views: : 10
- Total visitors : 5,443
- Total page views: 6,775
-
Recent Posts
- በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተያዘው የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ21 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ።
- ከፌደራል፣ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ስራ አስፈጻሚዎች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ንቅናቄና የብልፅግና ትሩፋት ለወጣቶች ተጠቃሚነት በሚል በጉራጌ ዞን ከእምድብር ከተማ አስተዳደርና ከቸሃ ወረዳ ወጣቶች ጋር የልምድ ልውውጥ ተካሄደ።
- የትምህርት መሰረተ ልማትና ግብአት ማሟላት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ሚናው የላቀ መሆኑን የኢፌድሪ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ።
- (no title)
- ሐምሌ 14/2016 ዓመተ ምህረት ታላቁ የጎዳና ላይ የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድም ታዉቋል ።
Archives
- July 2024
- June 2024
- May 2024
- April 2024
- March 2024
- February 2024
- January 2024
- July 2023
- June 2023
- May 2023
- April 2023
- March 2023
- January 2023
- November 2022
- October 2022
- September 2022
- August 2022
- July 2022
- May 2022
- April 2022
- March 2022
- February 2022
- January 2022
- December 2021
- November 2021
- October 2021
- September 2021
- July 2021
Categories