መስከረም 26/2015
በጉራጌ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እና የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ተፈታኝ ተማሪዎች ሳይጉላሉ ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መድረሳቸው ተናገሩ።
ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲገቡ የተደረገላቸው አቀባበል እንዳስደሰታቸው ገልጸው መንግስት ደህንነታቸው ተጠብቆ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ያለጸጥታ ችግር እንዲፈተኑ ማድረጉ የተሻለ አቅም ያላቸው ተማሪዎች ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋቸዋል ብለዋል።
መንግስት ተማሪዎቹ በትራንስፖርት እጥረት ምክንያት ሳይጉላሉ እንዲደርሱ የትራንስፖርት አገልግሎት ማመቻቸቱ አስደሳች መሆኑን ገልጸዋል።
ከዩኒቨርስቲው በ50 ኪሎሜትር እርቀት የሚገኙ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲው የማጓጓዝ ተግባር በነገው እለት የሚይቀጥል ይሆናል።
ለተማሪዎች መልካም እድል ተመኝተናል፣