ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ ህገወጥነትን በመከላከል ከመንግስት ጎን ሊቆም እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው አሳሰቡ።

በከተማው በተጠናቀቀው በጀት አመት 1 መቶ 67 ሄክታር መሬት ማስመለስ መቻሉን ተጠቆመ። የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው እንዳለት ከዚህ በፊት የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስተካከል በተለይም የህዝብና የመንግስት መሬቶች ለህዝብ…

Continue reading

የጉራጌ ዞን አስተዳዳር ለዞኑ ህዝቦች እና ለመላው ኢትዮጵያዉያን እንኳን ለ2017 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱ ይገልፃል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በተጠናቀቀው በጀት አመት በሀገራችን በተለይም በዞናችን ህብረተሰባችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። በግብርና ፣ በትምህርት፣ በጤና በመንገድና በጸጥታው ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶች…

Continue reading

መጪው የሚከበሩ በዓላቶች በሰላም እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት መደረጉ የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ።

የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ እና የዞኑ ፖሊስ መምሪያ በጋራ በመሆን የዘመን መለወጫ እና የመስቀል በዓላቶች በሰላም እንዲጠናቀቁ በማስመልከት ከጸጥታ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ…

Continue reading

የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ፣ሴቶች ህፃናትና የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ በጋራ በመሆን የአዲስ አመት በዓል ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋርተዋል።

የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ መኩሪያ ተመስገን እንዳሉት መምሪያው አቅም ደካሞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋዉያን እና ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎችን በዓልን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ ወቅት ድጋፎችን እያደረገ…

Continue reading

ጳጉሜን 5 የነገ ቀን ምክንያት በማድረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አንደኛ አመት ምስረታ በዓል “በአዲስ ምዕራፍ በወል እሴት ወደ መስፈንጠር” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን በተለያዩ ዝግጅቶች በወልቂጤ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ በበዓሉ ተገኝተው እንዳሉት ከክልሉ ምስረታ ጋር ተያይዞ የነበረው የሰላም፣ ጸጥታ እንዲሁም…

Continue reading

የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አመታዊው የሴክተር ጉባዔና የቱሪዝም ንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ አካሄደ።

የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ መሰረት አመርጋ እንደገለፁት ያሉንን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች ተጠብቀው ለትውልድ ለማስተላለፍና ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻዎች ለማድረግ ማልማትና ማስተዋወቅ ይገባል ብለዋል። የጉራጌ ማህበረሰብ በባህል፣ በታሪክ…

Continue reading