Year: 2021
https://www.facebook.com/1545883085664415/posts/3052032435049465/
በጉራጌ ዞን የተጀመረው ጤፍን በክላስተር የማልማት ስራው አበረታች በመሆኑ በቀጣይም ለሌሎች አካባቢ አርሶ አደሮች ማስፋት እንደሚያስፈልግ የደቡብ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በወልቂጤ ከተማ የሚስተዋለው ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ 30 ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ ተጨማሪ ሁለት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች እንደሚቆፈሩ የዞኑ ውሃ ማዕድንና ኤነርጂ መምሪያ አስታትወቀ።
የጉራጌ ዞን መምህራን ማህበር ከመማር ማስተመሩ ጎን ለጎን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እያደረጉት ያለው ንቁ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የደቡብ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ።
በጉራጌ ዞን የኢንቨስትመንት ፍቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ተግባር የገቡ 335 ፕሮጀክቶች ከ4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ እንደቻሉ የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።
የዞኑ የኢንቨስትመንት ስትሪንግ ኮሚቴ የፕሮጀክቶቹ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል። በጉብኝቱ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ጀማል በዞኑ የእንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማበረታታት በዘርፉ የነበሩ የአሰራር ችግሮች በመቅረፍ አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ…