ህብረተሰቡ ለጀግናው የሀገር የመከላከያ ሠራዊት የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።በሰላማዊ ሰልፋ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፋት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማል እንደገለጹት በሀገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ያልተዋጠላቸው የውስጥና የውጭ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው ለውጡን ለማደናቀፍ ከመቼው ጊዜ በላይ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ላለፋት ዘጠኝ ወራት ሲካሄድ የነበረውን ህግ የማስከበር ዘመቻ ከሰኔ አጋማሽ ጀምሮ አርሶ አደሩ ሳይደናገር የእርሻ ስራውን እንዲያከናውን እንዲሁም የትግራይ ህዝብ በአሸባሪው ህወኃት ቡድን ላይ የያዘውን ያልተገባ አቋም መለስ ብሎ እንዲያጤን ጊዜ ለመስጠት በማሰብ መንግስት የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ ማሳለፋን የገለጹት አቶ መሀመድ ጀማል ጁንታው ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በየበረሃው ተበትኖ የነበረውን ሀይሉን በማሰባሰብ እና ለውትድርና እድሜያቸው ያልደረሱ ልጆች በማሰለፍ በአፋርና በአማራ ክልሎች መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን ተናግረዋል።አሸባሪው የህወኃት ቡድን በአፋር ክልል ግላኮማ በሚባል ቦታ ቀደም ሲል በማይካድራ የፈጸመውን አይነት በንጹኃን ዜጎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ መፈጸሙ የጭካኔ ጥጉን የሚያሳይና ታሪክ ይቅር የማይለው መሆኑን አቶ መሀመድ ገልጸዋል።የዞኑ ህብረተሰብ በሀገር ላይ የተቃጣውን ጥቃት ለመመከት ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ከመንግስትና ከጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን 483 ሰንጋ በሬዎች፣ 6 ሚሊዮን የሚገመት የቁሳቁስ፣ 15 ሚሊዮን የጥሬ ብር በአጠቃላይ ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረግ መቻሉን የገለጹት አቶ መሀመድ ጀማል በቀጣይም የሚደረገውን ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ነስሩ ጀማል በበኩላቸው የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የጥፋት እጃቸው በሀገራችን በመሰንዘር ላይ ይገኛሉ ብለዋል።የጁንታው ሀገር የማፈራረስ አላማ በጀግናው የመከላከያ ሀይልና በህዝባችን በተባበረ ክንድ መክተን ግብዓተ መሬቱ ለመፈጸም ከመቼው ጊዜ በላይ ቆርጠን ተነስተናል ሲሉ አቶ ነስሩ ተናግረዋል።የሰልፋ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በሀገራችን ላይ የተቃጣውን የውጭ ጫና በመቃወም እንዲሁም አሸባሪው የህወኃት ቡድን በሰላማዊ ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጥቃት የሚወገዝ ነው ብለዋል።አክለወም ሰልፈኞቹ እንደገለጹት ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን በመሆን አሸባሪው የህወኃት ቡድን ለመደምሰስ በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት በአካል በመዝመት የሚጠበቅባቸውን በማድረግ የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።
- Our Visitor
- Today's visitors: 3
- Today's page views: : 4
- Total visitors : 5,412
- Total page views: 6,737
-
Recent Posts
- በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተያዘው የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ21 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ።
- ከፌደራል፣ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ስራ አስፈጻሚዎች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ንቅናቄና የብልፅግና ትሩፋት ለወጣቶች ተጠቃሚነት በሚል በጉራጌ ዞን ከእምድብር ከተማ አስተዳደርና ከቸሃ ወረዳ ወጣቶች ጋር የልምድ ልውውጥ ተካሄደ።
- የትምህርት መሰረተ ልማትና ግብአት ማሟላት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ሚናው የላቀ መሆኑን የኢፌድሪ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ።
- (no title)
- ሐምሌ 14/2016 ዓመተ ምህረት ታላቁ የጎዳና ላይ የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድም ታዉቋል ።
Archives
- July 2024
- June 2024
- May 2024
- April 2024
- March 2024
- February 2024
- January 2024
- July 2023
- June 2023
- May 2023
- April 2023
- March 2023
- January 2023
- November 2022
- October 2022
- September 2022
- August 2022
- July 2022
- May 2022
- April 2022
- March 2022
- February 2022
- January 2022
- December 2021
- November 2021
- October 2021
- September 2021
- July 2021
Categories