የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን የስፖርት ባለሞያዎችና የስፖርት ሳይንስ ተማሪዎችን የአንደኛ ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና በወልቂጤ የኒቨርሲቲ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀን መስጠት ተጀምረዋል። ዩኒቨርስቲው ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የስፖርት ልማት ዘርፉን ለማስፋፋትና ለመደገፍ በቅርበት ይሰራል። የጉራጌ ዞን ወጣቶችና እስፖርት መምሪያ ምክትል ኃላፊና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አደም ሽኩር በስልጠናው ማስጀመሪያ ወቀት እንደገለጹት መምሪያዉ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሶስት የስፖርት አይነቶች በአትሌቲክስ፣በቅርጫት ኳስና በቮሊቦል የስፖርት አይነቶች የአንደኛ ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ሳምንት እንደሚሰጥም ተናግረዋል። ስልጠናው ያስፈለገበት ዋናው አላማ ዞኑን በሁሉም የስፖርት አይነቶ ተሳታፊ ለማድረግና የአሰልጣኞች የአቅም ውስንነት በመቅረፍና በስፖርት ዘርፎች አመረቂ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሆነም ገልጸዋል ። አቶ አደም ሽኩር አክለውም በእውቀት የዳበር አሰልጣኞችን በማፍራት ታዳጊ ስፖርተኞችን ታች ወረዶ በማሰልጠንና በማብቃት በሀገር እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትኩርት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመላክተዋል ። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀብቴ ዱላ በስልጠናው ማስጀመሪያ ወቅት እንዳሉት ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ ያገኟቸውን እውቀቶች ወደ ተግባር የሚቀይሩበትና ትልቅ አቅም የሚያገኙበት እንደሆነም አስታዉቀዋል። ስልጠናው ለተከታታይ 15 ቀን እንደሚቆይና ሰልጣኞች በቆይታቸው የሚጠበቅባቸውን እውቀት በመቅሰም በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር መቅረፍ እንደሚገባቸዉም አሳስበዋል። የዩኒቨርሲቲዉ የስፖርት ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዶከተር አብዱላዚዝ ሙሰማ በበኩላቸዉ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ጋር በቅንጅት በመሆን በስፖርቱ ዘርፍ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰሩ መቆየቱም ተናግረዋል። በተጨማሪም ዩኒቨርስቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የስፖርት ልማት ዘርፍን ለማስፋፋትና ለመደገፍ በቅርበት እንደሚሰራም ተናግረዋል ። በዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የሚገኙ መዋቅሮች በእያንዳንዱ የስፖርት አይነት የተውጣጡ አሰልጣኞች፣ክለቦች ውስጥ ያሉ ስፖርተኞችና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት ሳይንስ ተማሪች በስልጠናው እየተሳተፉ ይገኛል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።በመረጃ ምንጭነት ገፃችን ምርጫዎ ስላደረጉ እናመሰግናለን! = ኢትዮጵያን እናልማ! = የፈረሰውን እንገንባ! = ለፈተና እንዘጋጅ! በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡ Facebook:- https://www.facebook.com/gurage1Zone Website:- https://gurage.gov.et Telegram:- https://t.me/comminuca Youtub: –https://www.youtube.com/channel/UCzrcazGvvIO2tG7bQN
- Our Visitor
- Today's visitors: 8
- Today's page views: : 10
- Total visitors : 5,428
- Total page views: 6,755
-
Recent Posts
- በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተያዘው የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ21 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ።
- ከፌደራል፣ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ስራ አስፈጻሚዎች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ንቅናቄና የብልፅግና ትሩፋት ለወጣቶች ተጠቃሚነት በሚል በጉራጌ ዞን ከእምድብር ከተማ አስተዳደርና ከቸሃ ወረዳ ወጣቶች ጋር የልምድ ልውውጥ ተካሄደ።
- የትምህርት መሰረተ ልማትና ግብአት ማሟላት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ሚናው የላቀ መሆኑን የኢፌድሪ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ።
- (no title)
- ሐምሌ 14/2016 ዓመተ ምህረት ታላቁ የጎዳና ላይ የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድም ታዉቋል ።
Archives
- July 2024
- June 2024
- May 2024
- April 2024
- March 2024
- February 2024
- January 2024
- July 2023
- June 2023
- May 2023
- April 2023
- March 2023
- January 2023
- November 2022
- October 2022
- September 2022
- August 2022
- July 2022
- May 2022
- April 2022
- March 2022
- February 2022
- January 2022
- December 2021
- November 2021
- October 2021
- September 2021
- July 2021
Categories